መዝሙር 110

መሲሑ ንጉሥና ካህን

የዳዊት መዝሙር

1 እግዚአብሔርጌታዬን፣

“ጠላቶችህን ለእግርህ መርገጫ፣

እስከማደርግልህ ድረስ፣

በቀኜ ተቀመጥ” አለው።

2 እግዚአብሔርብርቱ በትርህን ከጽዮን ወደ ውጭ ይሰዳል፤

አንተም በጠላቶችህ መካከል ሆነህ ትገዛለህ።

3 ለጦርነት በምትወጣበት ቀን፣

ሰራዊትህ በገዛ ፈቃዱ በጐንህ ይቆማል፤

ከንጋት ማሕፀን፣

በቅዱስ ግርማ ደምቀህ፣

የጐልማሳነትህን ልምላሜእንደ ጠል ትቀበላለህ።

4 “እንደ መልከጼዴቅ ሥርዐት፤

አንተ ለዘላለም ካህን ነህ” ብሎ፣

እግዚአብሔርምሎአል፤

እርሱ ሐሳቡን አይለውጥም።

5 ጌታ በቀኝህ ነው፤

በቍጣውም ቀን ነገሥታትን ያደቃቸዋል።

6 በሕዝቦች መካከል ይፈርዳል፤

በየአገሩ ያሉትንም ራሶች ከስክሶ ሬሳ በሬሳ ያደርጋቸዋል።

7 መንገድዳር ካለች ፈሳሽ ውሃ ይጠጣል፤

ስለዚህ ራሱን ቀና ያደርጋል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *