መዝሙር 111

ለመለኮቱ ባሕርያት የቀረበ ጸሎት

1 ሃሌ ሉያ።

በቅኖች ሸንጎ፣ በጉባኤም መካከል፣

ለእግዚአብሔርበፍጹም ልቤ ምስጋና አቀርባለሁ።

2 የእግዚአሔርሥራ ታላቅ ናት፤

ደስ የሚሰኙባትም ሁሉ ያውጠነጥኗታል።

3 ሥራው ባለ ክብርና ባለ ግርማ ነው፤

ጽድቁም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

4 ድንቅ ሥራው ሲታወስ እንዲኖር አደረገ፤

እግዚአብሔርቸር፣ ርኅሩኅም ነው።

5 ለሚፈሩት ምግብን ይሰጣል፤

ኪዳኑንም ለዘላለም ያስባል።

6 ለሕዝቡ የአሕዛብን ርስት በመስጠት፣

የአሠራሩን ብርታት አሳይቶአል።

7 የእጁ ሥራ እውነተኛና ቅን ነው፤

ሥርዐቱም ሁሉ የታመነ ነው፤

8 ከዘላለም እስከ ለዘላለም የጸና ነው፤

በእውነትና በቅንነትም የተሠራ ነው።

9 ለሕዝቡ መዳንን ሰደደ፤

ኪዳኑንም ለዘላለም አዘዘ፤

ስሙም የተቀደሰና የተፈራ ነው።

10 እግዚአብሔርንመፍራት የጥበብ መጀመሪያ ነው፤

ትእዛዙንም የሚፈጽሙ ጥሩ ማስተዋል አላቸው፤

ምስጋናውም ለዘላለም ይኖራል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *