መዝሙር 112

የጻድቅ ሰው ባሕርይ

1 ሃሌ ሉያ።

እግዚአብሔርንየሚፈራ፣

በትእዛዙም እጅግ ደስ የሚሰኝ የተባረከ ነው።

2 ዘሩ በምድር ላይ ኀያል ይሆናል፤

የቅኖች ትውልድ ትባረካለች።

3 ሀብትና ብልጽግና በቤቱ ይሞላል፤

ጽድቁም ለዘላለም ይኖራል።

4 ቸር፣ ርኅሩኅና ጻድቅ እንደ መሆኑ፣

ለቅን ሰው በጨለማ ውስጥ ብርሃን ይወጣለታል።

5 ለጋስና ያለ ማንገራገር የሚያበድር፣

ሥራውንም በትክክል የሚያከናውን ሰው መልካም ይሆንለታል፤

6 ለዘላለም ከስፍራው አይናወጥምና፤

ጻድቅ ሰውሲታወስ ይኖራል።

7 ክፉ ወሬ አያሸብረውም፤

ልቡእግዚአብሔርንበመተማመን የጸና ነው።

8 ልቡ የጸና ነው፤ አይፈራምም፤

በመጨረሻም የጠላቶቹን ውድቀት ያያል።

9 በልግስና ለድኾች ሰጠ፤

ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል፤

ቀንዱምበክብር ከፍ ከፍ ይላል።

10 ክፉ ሰው ይህን በማየት ይበሳጫል፤

ጥርሱን ያፋጫል፤ እየመነመነም ይጠፋል፤

የክፉዎችም ምኞት ትጠፋለች።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *