መዝሙር 113

ለታላቁና ለመሓሪው ጌታ ምስጋና

1 ሃሌ ሉያ።

የእግዚአብሔርአገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

የእግዚአብሔርንስም አወድሱ።

2 ከአሁን እስከ ዘላለም፣

የእግዚአብሔርስም የተመሰገነ ይሁን።

3 ከፀሓይ መውጫ እስከ መግቢያው ድረስ፣

የእግዚአብሔርስም የተመሰገነ ይሁን።

4 እግዚአብሔርከሕዝቦች ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ነው፤

ክብሩም ከሰማያት በላይ ነው።

5 እንደ አምላካችን እንደእግዚአብሔር፣

በላይ በዙፋኑ የተቀመጠ ማን ነው?

6 በሰማይና በምድር ያሉትንስ ለማየት፣

ራሱን ወደ ታች ዝቅ የሚያደርግ ማን ነው?

7 ድኻውን ከትቢያ ያነሣል፤

ችግረኛውን ከዐመድ ከፍ ከፍ ያደርጋል፤

8 ከመኳንንትም እኩል ስፍራ ይሰጠዋል፤

ከሕዝቡም ሹማምት ጋር ያስቀምጠዋል።

9 መካኒቱን ሴት በቤት ያኖራታል፤

ደስተኛም የልጆች እናት ያደርጋታል።

ሃሌ ሉያ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *