መዝሙር 114

ለፋሲካ የቀረበ ውዳሴ

1 እስራኤል ከግብፅ ወጥቶ ሲሄድ፣

የያዕቆብም ቤት ቋንቋው ልዩ ከሆነ ሕዝብ ተለይቶ ሲወጣ፣

2 ይሁዳየእግዚአብሔርመቅደስ፣

እስራኤልም ግዛቱ ሆነ።

3 ባሕር አየች፤ ሸሸችም፤

ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ።

4 ተራሮች እንደ አውራ በግ፣

ኰረብቶችም እንደ ጠቦት ዘለሉ።

5 አንቺ ባሕር፤ የሸሸሽው አንቺም ዮርዳኖስ ያፈገፈግሽው ለምንድን ነው?

6 እናንተ ተራሮች እንደ አውራ በግ፣

ኰረብቶችም እንደ ጠቦት ለምን ዘለላችሁ?

7 ምድር ሆይ፤ በጌታ ፊት፣

በያዕቆብ አምላክ ፊት ተንቀጥቀጪ፤

8 እርሱ ዐለቱን ወደ ኩሬ፤

ቋጥኙንም ወደ ውሃ ምንጭ ለወጠ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *