የእስራኤል አዳኝ
የዳዊት መዝሙረ መዓርግ
1 እስራኤል እንዲህ ይበል፦
“እግዚአብሔርከእኛ ጋር ባይሆን ኖሮ፣
2 ሰዎች በእኛ ላይ በተነሡ ጊዜ፣
እግዚአብሔርከእኛ ጋር ባይሆን ኖሮ፣
3 ቍጣቸው በላያችን በነደደ ጊዜ፣
በቁመናችን በዋጡን ነበር፤
4 ጐርፍ ባጥለቀለቀን፣
ፈረሰኛው ውሃ ባሰጠመን፣
5 ደራሽ ውሃም ጠራርጎ በወሰደን ነበር።
6 በጥርሳቸው ከመዘንጠል የጠበቀን፣
እግዚአብሔርይባረክ።
7 ነፍሳችን እንደ ወፍ፣
ከዐዳኝ ወጥመድ አመለጠች፤
ወጥመዱ ተሰበረ፤
እኛም አመለጥን።
8 የሰማይና የምድር ፈጣሪ፣
የእግዚአብሔርስም ረዳታችን ነው።