መዝሙር 125

እግዚአብሔር የሚታመኑበትን ይጠብቃል

መዝሙረ መዓርግ

1 በእግዚአብሔርየሚታመኑ፣

ሳትናወጥ ለዘላለም እንደምትኖር እንደ ጽዮን ተራራ ናቸው።

2 ተራሮች ኢየሩሳሌምን እንደ ከበቧት፣

ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም፣እግዚአብሔርበሕዝቡ ዙሪያ ነው።

3 ጻድቃን እጃቸውን፣ ለክፋት እንዳያነሡ፣

የክፉዎች በትረ መንግሥት፣

ለጻድቃን በተመደበች ምድር ላይ አያርፍም።

4 እግዚአብሔርሆይ፤ መልካም ለሆኑ፣

ልባቸውም ለቀና መልካም አድርግ።

5 ወደ ጠማማ መንገዳቸው የሚመለሱትን ግን፣

እግዚአብሔርከክፉ አድራጊዎች ጋር ያስወግዳቸዋል።

በእስራኤል ላይ ሰላም ይውረድ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *