መዝሙር 129

በጽዮን ጠላቶች ላይ የቀረበ ጸሎት

መዝሙረ መዓርግ

1 እስራኤል እንዲህ ይበል፦

“ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ፤

2 በርግጥ ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ፤

ዳሩ ግን ድል አላደረጉኝም።

3 ዐራሾች ጀርባዬን ዐረሱት፤

ትልማቸውንም አስረዘሙት።”

4 እግዚአብሔርግን ጻድቅ ነው፤

የክፉዎችን ገመድ በጣጥሶ ጣለው።

5 ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ፣

ዐፍረው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።

6 ገና ከመብቀሉ እንደሚደርቅ፣

በጣራ ላይ እንደ በቀለ ሣር ይሁኑ፤

7 ደግሞም ለዐጫጅ እጁን፣

ለነዶ ሰብሳቢ ዕቅፉን እንደማይሞላ ይሁኑ።

8 መንገድ ዐላፊዎችም፣

“የእግዚአብሔርበረከት በእናንተ ላይ ይሁን፤

በእግዚአብሔርስም እንባርካችኋለን” አይበሉ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *