መዝሙር 13

በአምላኩ የታመነ ሰው አቤቱታ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1 እግዚአብሔርሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ለዘላለሙ ትረሳኛለህ?

ፊትህንስ ከእኔ የምትሰውረው እስከ መቼ ድረስ ነው?

2 ከሐሳቤ ጋር የምሟገተው፣

ልቤም ቀኑን ሙሉ የሚያዝነው እስከ መቼ ነው?

ጠላቴስ በእኔ ላይ የሚያይለው እስከ መቼ ድረስ ነው?

3 እግዚአብሔርአምላኬ ሆይ፤ ተመልከት፤

ስማኝም፤

የሞት እንቅልፍ እንዳልተኛ ዐይኖቼን አብራ፤

4 በዚህም ጠላቴ፣ “አሸነፍሁት” እንዳይል፣

ባላጋራዎቼም በውድቀቴ ደስ እንዳይላቸው ርዳኝ።

5 እኔ ግን በጸናች ፍቅርህ እታመናለሁ፤

ልቤም በማዳንህ ደስ ይለዋል።

6 ቸርነቱ በዝቶልኛልና፣

ለእግዚአብሔርእዘምራለሁ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *