የግዞተኞች ቅኔ
1 በባቢሎን ወንዞች አጠገብ፣ በዚያ ተቀምጠን ሳለን፣
ጽዮን ትዝ ባለችን ጊዜ አለቀስን።
2 እዚያም በአኻያ ዛፎች ላይ፣
በገናዎቻችንን ሰቀልን።
3 የማረኩን በዚያ እንድንዘምርላቸው ጠየቁን፤
የሚያሠቃዩን የደስታ ዜማ ፈለጉብን፤
ደግሞም፣ “ከጽዮን መዝሙሮች አንዱን ዘምሩልን” አሉን።
4 የእግዚአብሔርንዝማሬ፣
እንዴት በባዕድ ምድር እንዘምር!
5 ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ብረሳሽ፣
ቀኝ እጄ ትክዳኝ።
6 ሳላስታውስሽ ብቀር፣
ኢየሩሳሌምን የደስታዬ ቍንጮ ባላደርግ፣
ምላሴ ከትናጋዬ ጋር ትጣበቅ።
7 እግዚአብሔርሆይ፤ ኢየሩሳሌም በወደቀችበት ቀን፣
ኤዶማውያን እንዴት እንደ ዛቱ ዐስብ፤
ደግሞም፣ “አፍርሷት፤
ፈጽማችሁ አፈራርሷት!” አሉ።
8 አንቺ አጥፊ የሆንሽ የባቢሎን ልጅ ሆይ፤
በእኛ ላይ ስለ ፈጸምሺው ድርጊት፣
የእጅሽን የሚሰጥሽ የተመሰገነ ነው፤
9 ሕፃናትሽንም ይዞ፣
በዐለት ላይ የሚፈጠፍጥ የተመሰገነ ነው።