መዝሙር 14

አምላክ የለሽ ሰዎች

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1 ሞኝበልቡ፣

“እግዚአብሔር የለም” ይላል።

ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤

በጎ ነገር የሚሠራ አንድም የለም።

2 የሚያስተውል፣ እግዚአብሔርን የሚፈልግ መኖሩን ለማየት፣

እግዚአብሔርከሰማይ ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።

3 ሁሉም ከመንገድ ወጥተዋል፤

በአንድ ላይም ብልሹ ሆነዋል፤

አንድ እንኳ፣

መልካም የሚያደርግ የለም።

4 የእግዚአብሔርንስም የማይጠሩት፣

ሕዝቤን እንደ እንጀራ የሚበሉት፣

ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ዕውቀት የላቸውምን?

5 ባሉበት ድንጋጤ ውጦአቸዋል፤

እግዚአብሔር በጻድቃን መካከል ይገኛልና።

6 እናንተ የድኾችን ዕቅድ ለማፋለስ ትሻላችሁ፤

እግዚአብሔርግን መጠጊያቸው ነው።

7 ምነው እስራኤልን የሚያድን ከጽዮን በወጣ!

እግዚአብሔርየሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣

ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤልም ሐሤት ያድርግ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *