መዝሙር 142

የሚታደን ሰው ጸሎት

ዋሻ ውስጥ በነበረ ጊዜ፤ የዳዊት ትምህርት፤

ጸሎት

1 ድምፄን ከፍ አድርጌ ወደእግዚአብሔርእጮኻለሁ፤

ድምፄን ከፍ አድርጌ ወደእግዚአብሔርልመና አቀርባለሁ።

2 ብሶቴን በፊቱ አፈስሳለሁ፤

ችግሬንም በፊቱ እናገራለሁ።

3 መንፈሴ በውስጤ ሲዝል፣

መንገዴን የምታውቅ አንተ ነህ፤

በመተላለፊያ መንገዴ ላይ፤

ወጥመድ በስውር ዘርግተውብኛል።

4 ወደ ቀኜ ተመልከት፤ እይም፤

ስለ እኔ የሚገደው የለም፤

ማምለጫም የለኝም፤

ስለ ነፍሴም ደንታ ያለው የለም።

5 እግዚአብሔርሆይ፤ ወደ አንተ እጮኻለሁ፤

ደግሞም፣ “አንተ መጠጊያዬ ነህ፤

በሕያዋንም ምድር ዕድል ፈንታዬ ነህ” እላለሁ።

6 እጅግ ተስፋ ቈርጫለሁና፣

ጩኸቴን ስማ፤

ከዐቅም በላይ ሆነውብኛልና፣

ከሚያሳድዱኝ አድነኝ።

7 ስምህን አመሰግን ዘንድ፣ ነፍሴን ከወህኒ አውጣት፤

ከምታደርግልኝም በጎ ነገር የተነሣ፣

ጻድቃን በዙሪያዬ ይሰበሰባሉ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *