መዝሙር 146

ለረድኤት አምላክ ምስጋና

1 ሃሌ ሉያ።

ነፍሴ ሆይ፤እግዚአብሔርንባርኪ።

2 በምኖርበት ዘመን ሁሉእግዚአብሔርን

አመሰግናለሁ፤

በሕይወትም እስካለሁ ለአምላኬ እዘምራለሁ።

3 በገዦች አትታመኑ፤ ማዳን በማይችሉ ሥጋ ለባሾችም አትመኩ።

4 መንፈሳቸው ትወጣለች፤ ወደ መሬታቸውም ይመለሳሉ፤

ያን ጊዜም ዕቅዳቸው እንዳልነበር ይሆናል።

5 ረዳቱ የያዕቆብ አምላክ የሆነ፣

ተስፋውንም በአምላኩበእግዚአብሔርላይ የጣለ ሰው ምስጉን ነው፤

6 እርሱ ሰማይንና ምድርን፣ ባሕርንም፣

በእነዚህም ውስጥ ያለውን ሁሉ የፈጠረ፣

ታማኝነቱንም ለዘላለም የሚጠብቅ ነው፤

7 ለተበደሉት የሚፈርድ፣

ለተራቡት ምግብን የሚሰጥ እርሱ ነው፤

እግዚአብሔርእስረኞችን ከእስራት ያወጣል፤

8 እግዚአብሔርየዕዉራንን ዐይን ያበራል፤

እግዚአብሔርየተዋረዱትን ከፍ ያደርጋል፤

እግዚአብሔርጻድቃንን ይወዳል፤

9 እግዚአብሔርስደተኞችን ይጠብቃል፤

ድኻ ዐደጎችንና መበለቶችን ይደግፋል፤

የክፉዎችን መንገድ ግን ያጠፋል።

10 እግዚአብሔርለዘላለም ይነግሣል፤

ጽዮን ሆይ፤ አምላክሽ ለትውልድ ሁሉ ንጉሥ ነው።

ሃሌ ሉያ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *