መዝሙር 15

የእግዚአብሔር ቤተኛ

የዳዊት መዝሙር

1 እግዚአብሔርሆይ፤ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል?

በተቀደሰው ኰረብታህስ ማን መኖር ይችላል?

2 አካሄዱ ንጹሕ የሆነ፣

ጽድቅን የሚያደርግ፤

ከልቡ እውነትን የሚናገር፤

3 በምላሱ የማይሸነግል፤

በባልንጀራው ላይ ክፉ የማይሠራ፤

ወዳጁን የማያማ፤

4 ነውረኛ በፊቱ የተናቀ፤

እግዚአብሔርንየሚፈሩትን ግን የሚያከብር፤

ዋጋ የሚያስከፍለውም ቢሆን፣

ቃለ መሐላውን የሚጠብቅ፤

5 ገንዘቡን በዐራጣ የማያበድር፣

በንጹሓን ላይ ጒቦ የማይቀበል፤

እነዚህን የሚያደርግ፣

ከቶ አይናወጥም።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *