መዝሙር 24

ወደ መቅደስ መግቢያ ጸሎት

የዳዊት መዝሙር

1 ምድርና በእርሷ ያለው ሁሉ፣

ዓለምና በውስጧ የሚኖር ሁሉየእግዚአብሔርነው፤

2 እርሱ በባሕሮች ላይ መሥርቶአታልና፤

በውሆችም ላይ አጽንቶአታል።

3 ወደእግዚአብሔርተራራ ማን ሊወጣ ይችላል?

በተቀደሰ ስፍራውስ ማን ይቆማል?

4 ንጹሕ እጅና ቅን ልብ ያለው፤

ነፍሱን ለሐሰት ነገር የማያስገዛ፤

በውሸት የማይምል፤

5 እርሱ በረከትንከእግዚአብሔርዘንድ፣

ምሕረትንም ከአዳኝ አምላኩ ይቀበላል።

6 እርሱን የሚፈልግ ትውልድ እንዲህ ነው፤

የያዕቆብ አምላክ ሆይ፤ ፊትህንየሚፈልግ እንዲህ ያለ ነው።ሴላ

7 እናንተ ደጆች፤ ቀና በሉ፤

እናንተ የዘላለም በሮች፤

የክብር ንጉሥ እንዲገባ ብድግ በሉ!

8 ይህ የክብር ንጉሥ ማን ነው?

እግዚአብሔርነው ብርቱና ኀያል፤

እግዚአብሔርነው በውጊያ ኀያል።

9 እናንተ ደጆች፤ ቀና በሉ፤

እናንተ የዘላለም በሮች፤

የክብር ንጉሥ እንዲገባ ብድግ በሉ!

10 ይህ የክብር ንጉሥ ማን ነው?

የሰራዊትአምላክ፣

እርሱ የክብር ንጉሥ ነው።ሴላ

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *