መዝሙር 29

ለማዕበሉ ጌታ የቀረበ ውዳሴ

የዳዊት መዝሙር

1 እናንተ ኀያላን፣ለእግዚአብሔርስጡ፤

ክብርንና ብርታትንለእግዚአብሔርስጡ።

2 ለስሙ የሚገባ ክብርለእግዚአብሔርስጡ፤

በቅድስናው ግርማለእግዚአብሔርስገዱ።

3 የእግዚአብሔርድምፅ በውሆች ላይ ነው፤

የክብር አምላክ አንጐደጐደ፤

እግዚአብሔርበታላላቅ ውሆች ላይ አንጐደጐደ።

4 የእግዚአብሔርድምፅ ኀያል ነው፤

የእግዚአብሔርድምፅ ግርማዊ ነው።

5 የእግዚአብሔርድምፅ ዝግባን ይሰብራል፤

እግዚአብሔርየሊባኖስን ዝግባ ይሰባብራል።

6 ሊባኖስን እንደ ጥጃ፣

ስርዮንንምእንደ አውራሪስ ግልገል ያዘልላል።

7 የእግዚአብሔርድምፅ

የእሳት ነበልባል ይረጫል።

8 የእግዚአብሔርድምፅ ምድረ በዳውን ያናውጣል፤

የእግዚአብሔርድምፅ የቃዴስን ምድረ በዳ ያናውጣል።

9 የእግዚአብሔርድምፅ ወርካዎችን ይወዘውዛል፤

ጫካዎችንም ይመነጥራል፤

ሁሉም በእርሱ ቤተ መቅደስ ሆኖ “ይክበር!” ይላል።

10 እግዚአብሔርበጐርፍ ላይ ዙፋኑን ዘርግቶ ተቀምጦአል፤

እግዚአብሔርበንጉሥነቱ ለዘላለም በዙፋኑ ላይ ይቀመጣል።

11 እግዚአብሔርለሕዝቡ ብርታትን ይሰጣል፤

እግዚአብሔርሕዝቡን በሰላም ይባርካል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *