መዝሙር 54

ለፍትሕ አምላክ የቀረበ አቤቱታ

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች፤ ዜፋውያን ወደ ሳኦል መጥተው፣ “ዳዊት በእኛ ዘንድ ተደብቆአል” ባሉት ጊዜ፤ የዳዊት ትምህርት።

1 እግዚአብሔር ሆይ፤ በስምህ አድነኝ፤

በኀይልህም ፍረድልኝ።

2 እግዚአብሔር ሆይ፤ ጸሎቴን ስማልኝ፤

የአፌንም ቃል አድምጥ።

3 ባዕዳን ተነሥተውብኛልና፤

ግፈኞች ነፍሴን ሽተዋታል፤

እግዚአብሔርንም ከምንም አልቈጠሩም።ሴላ

4 እነሆ፤ እግዚአብሔር ረዳቴ ነው፤

ጌታም ደግፎ ይይዘኛል።

5 የገዛ ክፋታቸው በሚያደቡብኝ ላይ ይመለስባቸው፤

በቃልህ ታማኝ ነህና አጥፋቸው።

6 በበጎ ፈቃድ መሥዋዕት እሠዋልሃለሁ፤

እግዚአብሔርሆይ፤ መልካም ነውና፣

ለስምህ ምስጋና አቀርባለሁ፤

7 ከመከራ ሁሉ ታድጎኛልና፤

ዐይኔም የጠላቶቼን ውድቀት ለማየት በቅቶአል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *