መዝሙር 70

የጭንቀት ጩኸት

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር፤ ለመታሰቢያ

1 አምላክ ሆይ፤ ታድነኝ ዘንድ ዘንበል በል፤

እግዚአብሔርሆይ፤ እኔን ለመርዳት ፍጠን።

2 ሕይወቴን ለማጥፋት የሚሹ፣

ይፈሩ፤ ሁከትም ይምጣባቸው፤ የእኔን መጐዳት የሚመኙ፣

በውርደት ወደ ኋላቸው ይመለሱ።

3 በእኔ ላይ፣ “እሰይ! እሰይ!” የሚሉ፣

ተሸማቀው ወደ ኋላ ይመለሱ።

4 ነገር ግን የሚሹህ ሁሉ፣

በአንተ ሐሤት ያድርጉ፤ ደስም ይበላቸው፤

“ማዳንህን የሚወዱ ሁሉ ሁል ጊዜ፣

እግዚአብሔር ከፍ ይበል!” ይበሉ።

5 እኔ ግን ምስኪንና ችግረኛ ነኝ፤

አምላክ ሆይ፤ ፈጥነህ ድረስልኝ፤

ረዳቴም፣ ታዳጊዬም አንተ ነህና፤

እግዚአብሔርሆይ፤ አትዘግይ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *