መዝሙር 87

ጽዮን የሕዝቦች እናት

የቆሬ ልጆች መዝሙር፤ ማሕሌት

1 መሠረቱን በተቀደሱ ተራሮች አቆመ፤

2 እግዚአብሔርከያዕቆብ ማደሪያዎች ሁሉ ይልቅ፣

የጽዮንን ደጆች ይወዳል።

3 የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ፤

ስለ አንቺ ክቡር የሆነ ነገር እንዲህ ተብሎ ይነገራል፤ሴላ

4 “ከሚያውቁኝ መካከል፣

ረዓብንናባቢሎንን እጠቅሳለሁ፤

እነሆ፤ ፍልስጥኤምና ጢሮስ ከኢትዮጵያ ጋር፣

‘ይህሰው በዚያ ነው የተወለደው’ ይላሉ።”

5 በእርግጥም ስለ ጽዮን፣

“ይህም ያም ሰው በእርሷ ውስጥ ተወለዱ፤

ልዑልም ራሱ ያጸናታል” ይባላል።

6 እግዚአብሔርሕዝቡን ሲመዘግብ፣

“ይህ ሰው የተወለደው በዚያ ነው” ብሎ ይጽፋል።ሴላ

7 የሚያዜሙም መሣሪያ የሚጫወቱም፣

“ምንጩ ሁሉ በአንቺ ውስጥ ይገኛል” ይላሉ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *