መዝሙር 98

የዓለም ሁሉ ዳኛ

መዝሙር

1 ለእግዚአብሔርአዲስ ዝማሬ አቅርቡ፤

እርሱ ድንቅ ነገሮችን አድርጎአልና፤

ቀኝ እጁ፣ ቅዱስ ክንዱም፣

ማዳንን አድርገውለታል።

2 እግዚአብሔርማዳኑን አሳወቀ፤

ጽድቁንም በሕዝቦች ፊት ገለጠ።

3 ለእስራኤል ቤት ምሕረቱን፣

ታማኝነቱንም አሰበ፤

የምድር ዳርቻዎችም ሁሉ፣

የአምላካችንን ማዳን አዩ።

4 ምድር ሁሉለእግዚአብሔርእልል በሉ፤

ውዳሴን አፍልቁ፤ በደስታና በዝማሬ አመስግኑ፤

5 ለእግዚአብሔርበገና ደርድሩለት፤

በበገናና በዝማሬ ድምፅ ዘምሩለት፤

6 በእንቢልታና በመለከት ድምፅ፣

በንጉሡበእግዚአብሔርፊት እልል በሉ።

7 ባሕርና በውስጧ ያለው ሁሉ፣

ዓለምና የሚኖሩባትም ሁሉ ያስገምግሙ።

8 ወንዞች በእጃቸው ያጨብጭቡ፤

ተራሮችም በአንድነት ይዘምሩ፤

9 እነዚህበእግዚአብሔርፊት ይዘምሩ፤

እርሱ በምድር ላይ ሊፈርድ ይመጣልና፤

በዓለም ላይ በጽድቅ፣

በሕዝቦችም ላይ በእውነት ይበይናል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *