መዝሙር 99

ጻድቅና ቅዱስ አምላክ

1 እግዚአብሔርነገሠ፤

ሕዝቦች ይንቀጥቀጡ፤

በኪሩቤል ላይ በዙፋን ተቀምጦአል፤

ምድር ትናወጥ።

2 እግዚአብሔርበጽዮን ታላቅ ነው፤

ከሕዝቦችም ሁሉ በላይ ከፍ ከፍ ብሎአል።

3 ታላቁንና አስፈሪውን ስምህን ይወድሱ፤

እርሱ ቅዱስ ነው።

4 ፍትሕን የምትወድ፣ ኀያል ንጉሥ ሆይ፤

አንተ ትክክለኝነትን መሠረትህ፤

ፍትሕንና ቅንነትንም፣

ለያዕቆብ አደረግህ።

5 አምላካችንንእግዚአብሔርንከፍ ከፍ አድርጉት፤

በእግሩ መርገጫ ስገዱ፤

እርሱ ቅዱስ ነውና።

6 ሙሴና አሮን ካህናቱ ከሆኑት መካከል ነበሩ፤

ሳሙኤልም ስሙን ከጠሩት መካከል አንዱ ነበረ፤

እነርሱ ወደእግዚአብሔርተጣሩ፤

እርሱም መለሰላቸው።

7 ከደመና ዐምድ ውስጥ ተናገራቸው፤

እነርሱም ሥርዐቱንና የሰጣቸውን ድንጋጌ ጠበቁ።

8 እግዚአብሔርአምላካችን ሆይ፤

አንተ መለስህላቸው፤

ጥፋታቸውንብትበቀልም እንኳ፣

አንተ ይቅር የምትላቸው አምላክ ነህ።

9 አምላካችንንእግዚአብሔርንከፍ ከፍ አድርጉት፤

በቅዱስ ተራራውም ላይ ስገዱ፤

አምላካችንእግዚአብሔርቅዱስ ነውና።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *