ኢሳይያስ 12

የውዳሴ መዝሙር

1 በዚያን ቀን እንዲህ ትላለህ፤

“እግዚአብሔርሆይ፤

ቀድሞ ተቈጥተኸኝ ነበር፤

አሁን ግን ከቍጣህ ተመለስህ፤

ደግሞም አጽናንተኸኛልና እወድስሃለሁ።

2 እነሆ፣ እግዚአብሔር ድነቴ ነው፤

እታመናለሁ፣ ደግሞም አልፈራም፤

ጌታእግዚአብሔርብርታቴና ዝማሬዬ ነው፤

ድነቴም ሆኖአል።”

3 ከድነቴ ምንጮች

ውሃ በደስታ ትቀዳላችሁ።

4 በዚያን ቀን እንዲህ ትላላችሁ፤

“እግዚአብሔርንአመስግኑ፤ ስሙንም ጥሩ፤

ያደረገውንም በአሕዛብ መካከል አስታውቁ፤

ስሙ ከፍ ከፍ ማለቱንም ዐውጁ።

5 ለእግዚአብሔርዘምሩ፤ ታላቅ ሥራ ሠርቶአልና፤

ይህም ለዓለም ሁሉ ይታወቅ።

6 የጽዮን ሕዝብ ሆይ፤ እልል በሉ፤

በደስታም ዘምሩ፤

በመካከላችሁ ያለው የእስራኤል ቅዱስ ታላቅ ነውና።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *