ዘካርያስ 13

ከኀጢአት መንጻት

1 “በዚያ ቀን የዳዊትን ቤትና የኢየሩሳሌምን ነዋሪዎች ከኀጢአትና ከርኵሰት የሚያነጻ ምንጭ ይከፈታል።

2 “በዚያ ቀን የጣዖታትን ስም ከምድሪቱ አጠፋለሁ፤ ከእንግዲህም አይታሰቡም” ይላልእግዚአብሔርጸባኦት። “ነቢያትንና ርኵስ መንፈስን ከምድሪቱ አስወግዳለሁ።

3 ማንም ትንቢት ቢናገር ወላጅ አባትና እናቱ፣ ‘በእግዚአብሔር ስም ሐሰት ተናግረሃልና ሞት ይገባሃል’ ይሉታል። ትንቢት ሲናገርም የገዛ ወላጆቹ ይወጉታል።

4 “በዚያን ቀን እያንዳንዱ ነቢይ ስለሚናገረው የትንቢት ራእይ ያፍራል፤ ለማታለልም የነቢያትን ጠጒራም ልብስ አይለብስም።

5 እርሱም፣ ‘እኔ ገበሬ እንጂ ነቢይ አይደለሁም፤ ከልጅነቴጀምሮ ኑሮዬ የተመሠረተውም በዕርሻ ላይ ነው’ ይላል።

6 አንድ ሰው፣ ‘ይህ በሰውነትህላይ ያለው ቊስል ምንድን ነው?’ ብሎ ቢጠይቀው፣ ‘በባልንጀሮቼ ቤት ሳለሁ የቈሰልሁት ነው’ ይላል።

እረኛው ተመታ፤ በጎቹ ተበተኑ

7 እግዚአብሔርጸባኦት እንዲህ ይላል፤

“ሰይፍ ሆይ፤ በእረኛዬ፣

በቅርብ ወዳጄ ላይ ንቃ!

እረኛውን ምታ፤

በጎቹ ይበተናሉ፤

እኔም ክንዴን ወደ ታናናሾቹ አዞራለሁ።

8 እግዚአብሔርእንዲህ ይላል፤ “የምድር ሁሉ፣

ሁለት ሦስተኛው ተመትቶ ይጠፋል፤

አንድ ሦስተኛው ግን በውስጡ ይቀራል፤

9 ይህን አንድ ሦስተኛውን ክፍል ወደ እሳት አመጣለሁ፤

እንደ ብር አነጥራቸዋለሁ፤

እንደ ወርቅም እፈትናቸዋለሁ፤

እነርሱ ስሜን ይጠራሉ፤

እኔም እመልስላቸዋለሁ፤

እኔም፣ ‘ሕዝቤ ናቸው’ እላለሁ፤

እነርሱም፣ ‘እግዚአብሔርአምላካችን ነው’ ይላሉ።”

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *