ዮናስ 2

የዮናስ ጸሎት

1 ዮናስ በዓሣው ሆድ ውስጥ ሆኖ ወደ አምላኩ ወደእግዚአብሔርጸለየ፤

2 እንዲህም አለ፤

“ተጨንቄ ሳለሁ ወደእግዚአብሔርተጣራሁ፤

እርሱም መለሰልኝ፤

ከመቃብሩምጥልቅ ርዳታን ፈልጌ ተጣራሁ፤

አንተም ጩኸቴን ሰማህ።

3 ጥልቅ ወደ ሆነው፣

ወደ ባሕሩ መካከል ጣልኸኝ፤

ፈሳሾችም ዙሪያዬን ከበቡኝ፤

ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ፣

በላዬ አለፉ።

4 እኔም፣ ‘ከፊትህ ጠፋሁ፣

ነገር ግን እንደ ገና፣

ወደ ቅዱስ መቅደስህ፣

እመለከታለሁ’ አልሁ።

5 ውሃ እስከ ዐንገቴ አጠለቀኝ፤

ጥልቁም ከበበኝ፤

የባሕርም ዐረም በራሴ ላይ ተጠመጠመ።

6 ወደ ተራሮች መሠረት ሰመጥሁ፤

የምድርም በር ለዘላለም ተዘጋብኝ፤

እግዚአብሔርአምላኬ ሆይ፤

አንተ ግን ሕይወቴን ከጒድጓድ አወጣህ።

7 “ነፍሴ በዛለች ጊዜ፣

እግዚአብሔርሆይ፤ አንተን ዐሰብሁ፤

ጸሎቴም ወደ አንተ፣

ወደ ቅዱስ መቅደስህ ዐረገች።

8 “ከንቱ በሆኑ ጣዖቶች ላይ የሚንጠለጠሉ፤

ሊያገኙ የሚገባቸውን ጸጋ ያጣሉ።

9 እኔ ግን በምስጋና መዝሙር፣

መሥዋዕት እሠዋልሃለሁ፤

የተሳልሁትንም እሰጣለሁ፤

ድነትከእግዚአብሔርዘንድ ነው።”

10 እግዚአብሔርምዓሣውን አዘዘው፤ ዮናስንም በደረቅ ምድር ላይ ተፋው።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *