የጻድቃን ትምክሕት
ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር
1 በእግዚአብሔርታምኛለሁ፤
ታዲያ ነፍሴን፣ “እንደ ወፍ ወደ ተራራ ብረሪ”
ለምን ትሏታላችሁ?
2 ደግሞም ለምን እንዲህ ትሉኛላችሁ?
“ክፉዎች፣ እነሆ፣ ቀስታቸውን ገትረዋል፤
የቅኑን ሰው ልብ በጨለማ ለመንደፍ፣
ፍላጻቸውን በአውታሩ ላይ ደግነዋል።
3 መሠረቱ ከተናደ፣
ጻድቅ ምን ማድረግ ይችላል?”
4 እግዚአብሔርበተቀደሰ መቅደሱ አለ፤
የእግዚአብሔርዙፋን በሰማይ ነው።
ዐይኖቹ ሰዎችን ይመለከታሉ፤
ቅንድቦቹም የሰው ልጆችን ይመረምራሉ።
5 እግዚአብሔርጻድቁንና ኀጥኡን ይመረምራል፤
ዐመፃን የሚወዱትን ግን፣
ነፍሱ ትጠላቸዋለች።
6 እርሱ በክፉዎች ላይ የእሳት ፍምና ዲን ያዘንባል፤
የጽዋቸውም ዕጣ ፈንታ፣
የሚለበልብ ዐውሎ ነፋስ ነው።
7 እግዚአብሔርጻድቅ ነውና፤
የጽድቅ ሥራም ይወዳል፤
ቅኖችም ፊቱን ያያሉ።