መዝሙር 12

ከክፉ ዓለም ለመዳን የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በስምንተኛው ቅኝት የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር።

1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ደግ ሰው የለምና አንተው ድረስልኝ!

ከሰዎችም መካከል አንድ ታማኝ አይገኝም።

2 እርስ በርሳቸው ውሸት ይነጋገራሉ፤

በሽንገላ ከንፈርና በሁለት ልብ ይናገራሉ፤

3 ሸንጋዩን ከንፈር ሁሉ፣

ነገር የምታበዛውንም ምላስእግዚአብሔርያጥፋ!

4 እነዚህም፣ “በአንደበታችን እንረታለን፤

ከንፈራችን የእኛ ነው፤ጌታችንስ ማነው?”

የሚሉ ናቸው።

5 እግዚአብሔር፣“ስለ ድኾች መከራ፣

ስለ ችግረኞችም ጩኸት፣

አሁን እነሣለሁ፤

በናፈቁትም ሰላም አኖራቸዋለሁ” ይላል።

6 የእግዚአብሔርቃል የጠራ ቃል ነው፤

ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ፣

በምድር ላይ በከውር እንደ ተፈተነ ብር ነው።

7 እግዚአብሔርሆይ፤ አንተ ትጠብቀናለህ፤

ከዚህም ትውልድ ለዘላለም ትከልለናለህ።

8 በሰዎች ዘንድ ክፋት ከፍ ከፍ ባለ ጊዜ፣

ዐመፀኞች በየአቅጣጫው በዛቻ ይዞራሉ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *