መዝሙር 4

የሠርክ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዜም የዳዊት መዝሙር

1 የጽድቄ አምላክ ሆይ፤

በጠራሁህ ጊዜ መልስልኝ፤

ከጭንቀቴ አሳርፈኝ፤

ማረኝ፤ ጸሎቴንም ስማ።

2 ሰዎች ሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ክብሬን ዝቅታደርጋላችሁ?

እስከ መቼስ ድረስ ከንቱ ነገርን ትወዳላችሁ? ሐሰትንስትሻላችሁ?ሴላ

3 እግዚአብሔርጻድቁን ለራሱ እንደ ለየ ዕወቁ፤

እግዚአብሔርወደ እርሱ በተጣራሁ ጊዜ ይሰማኛል።

4 ስትቈጡ ኀጢአት አትሥሩ፤

በዐልጋችሁም ላይ ሳላችሁ፣

ልባችሁን መርምሩ፤ ጸጥም በሉ።ሴላ

5 የጽድቅን መሥዋዕት አቅርቡ፤

በእግዚአብሔርምታመኑ።

6 ብዙዎች፣ “አንዳች በጎ ነገር ማን ያሳየናል? ይላሉ፤

እግዚአብሔርሆይ፤ የፊትህ ብርሃን በላያችን ይብራ።

7 ስንዴና አዲስ የወይን ጠጅ በብዛት ባመረቱ ጊዜ ከሚያገኙት ደስታ ይልቅ፣

አንተ ልቤን በታላቅ ሐሤት ሞልተኸዋል።

8 በሰላም እተኛለሁ፤ አንቀላፋለሁም፤

እግዚአብሔርሆይ፤ ያለ ሥጋት የምታሳድረኝ አንተ ብቻ ነህና።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *