መዝሙር 6

በጭንቅ ጊዜ የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር በሸሚኒት

1 እግዚአብሔርሆይ፤ በቍጣህ

አትገሥጸኝ፤

በመዓትህም አትቅጣኝ።

2 እግዚአብሔርሆይ፤ ዐቅመ ቢስ ነኝና ማረኝ፤

እግዚአብሔርሆይ፤ ዐጥንቶቼ ተናግተዋልና ፈውሰኝ።

3 ነፍሴ እጅግ ታውካለች፤

እስከ መቼ፤ አንተእግዚአብሔርሆይ፤ ይህ እስከ መቼ ድረስ ይሆናል?

4 እግዚአብሔርሆይ፤ ተመለስና ሕይወቴን ታደጋት፤

ስለ ጽኑ ፍቅርህም አድነኝ፤

5 በሞት የሚያስታውስህ የለምና፤

በሲኦልስማን ያመሰግንሃል?

6 ከመቃተቴ የተነሣ ዝያለሁ፤

ሌሊቱን ሁሉ በልቅሶ ዐልጋዬን አርሳለሁ፤

መኝታዬንም በእንባዬ አሾቃለሁ።

7 ዐይኖቼ በሐዘን ብዛት ደክመዋል፤

ከጠላቶቼም ሁሉ የተነሣ ማየት ተስኖአቸዋል።

8 እናንተ ክፉ አድራጊዎች ሁሉ፤ ከእኔ ራቁ፤

እግዚአብሔርየልቅሶዬን ድምፅ ሰምቶአልና።

9 እግዚአብሔርልመናዬን አድምጦአል፤

እግዚአብሔርጸሎቴን ይቀበላል።

10 ጠላቶቼ ሁሉ ያፍራሉ፤ እጅግም ይደነግጣሉ፤

በመጡበት ይመለሳሉ፤ ድንገትም ይዋረዳሉ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *