ኢሳይያስ 15

በሞዓብ ላይ የተነገረ ትንቢት

1 ስለ ሞዓብ የተነገረው ንግር ይህ ነው፤

የሞዓብ ዔር ፈራረሰች፤

በአንድ ሌሊትም ተደመሰሰች።

የሞዓብ ቂር ፈራረሰች፣

በአንድ ሌሊት ተደመሰሰች።

2 ዲቦን ወደ መቅደሱ ወጣ፤

ሊያለቅስም ወደ ኰረብታው ሄደ፤

ሞዓብ ስለ ናባው፣ ስለ ሜድባም ዋይታ ያሰማል፤

ራስ ሁሉ ተመድምዶአል፤

ጢምም ሁሉ ተላጭቶአል።

3 በየመንገዱም ማቅ ይለብሳሉ፤

በየሰገነቱና በየአደባባዩ

ሁሉም ያለቅሳሉ፤

እንባም ይራጫሉ።

4 ሐሴቦንና ኤልያሊ ጮኹ፤

ድምፃቸው እስከ ያሀድ ድረስ ተሰማ፤

ስለዚህ የሞዓብ ጦረኞች ጮኹ፤

ልባቸውም ራደ።

5 ልቤ ስለ ሞዓብ አለቀሰ፤

ስደተኞቿም እስከ ዞዓር፣

እስከ ዔግላት ሺሊሺያ ሸሹ፤

እንባቸውን እያፈሰሱ

ወደ ሉሒት ወጡ፤

በሖሮናይም መንገድም፣

ስለ ጥፋታቸው ዋይ እያሉ ነጐዱ።

6 የኔምሬ ውሆች ደርቀዋል፤

ሣሩ ጠውልጎአል፤

ቡቃያውም ጠፍቶአል፤

ለምለም ነገር አይታይም።

7 ስለዚህ ያገኙትን ሀብት፣

ያከማቹትን ንብረት ከአኻያ ወንዝ ማዶ ተሸክመው ያሻግሩታል።

8 ጩኸታቸው እስከ ሞዓብ ዳርቻ ድረስ ያስተጋባል፤

ዋይታቸው እስከ ኤግላይም፣

ሰቈቃቸውም እስከ ብኤርኢሊም ደረሰ።

9 የዲሞንወንዞች በደም ተሞልተዋል፤

በዲሞን ላይ ግን ከዚያ ነገር የበለጠ አመጣለሁ፤

ከሞዓብ በሚሸሹት፣

በምድሪቱም ላይ በሚቀሩት አንበሳ እሰድዳለሁ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *