መዝሙር 150

የምስጋና መዝሙር

1 ሃሌ ሉያ።

እግዚአብሔርንበመቅደሱ አመስግኑት፤

በታላቅ ጠፈሩ አወድሱት።

2 ስለ ብርቱ ሥራው አመስግኑት፤

እጅግ ታላቅ ነውና ወድሱት።

3 በመለከት ድምፅ አመስግኑት፤

በበገናና በመሰንቆ ወድሱት።

4 በከበሮና በሽብሸባ አመስግኑት፤

በባለ አውታር መሣሪያና በእምቢልታ አወድሱት።

5 ተርገብጋቢ ድምፅ ባለው ጸናጽል አመስግኑት፤

ድምፀ መልካም በሆነ ጸናጽል ወድሱት።

6 እስትንፋስ ያለው ሁሉእግዚእብሔርንያመስግን።

ሃሌ ሉያ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *