መዝሙር 149

የድል መዝሙር

1 ሃሌ ሉያ።

ለእግዚአብሔርአዲስ ቅኔ ተቀኙ፤

ምስጋናውንም በቅዱሳን ጉባኤ ዘምሩ።

2 እስራኤል በፈጣሪው ደስ ይበለው፤

የጽዮንም ልጆች በንጉሣቸው ሐሤት ያድርጉ።

3 ስሙን በሽብሰባ ያመስግኑ፤ በከበሮና በመሰንቆ ይዘምሩለት።

4 እግዚአብሔርበሕዝቡ ደስ ይለዋልና፤

የዋሃንንም በማዳኑ ውበት ያጐናጽፋል።

5 ቅዱሳን በዚህ ክብር ይጓደዱ፤

በመኝታቸውም ላይ እልል እያሉ ይዘምሩ።

6 የአምላክ ውዳሴ በአንደበታቸው፣

ባለ ሁለት ልሳን ሰይፍም በእጃቸው ይሁን፤

7 በዚህ ሕዝቦችን ይበቀላሉ፤

ሰዎችንም ይቀጣሉ፤

8 ነገሥታታቸውን በሰንሰለት፣

መኳንንታቸውንም በእግር ብረት ያስራሉ፤

9 ይህም በእነርሱ ላይ የተጻፈውን ፍርድ ለመፈጸም ነው።

ለቅዱሳኑም ሁሉ ይህች ክብር ናት።

ሃሌ ሉያ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *