መዝሙር 133

የወንድማማች ፍቅር

የዳዊት መዝሙረ መዓርግ

1 ወንድሞች ተስማምተው በአንድነት ሲኖሩ፣

እንዴት መልካም ነው! ምንኛስ ደስ ያሰኛል!

2 በራስ ላይ ፈሶ፣

እስከ ጢም እንደሚዘልቅ፣

እስከ አሮን ጢም እንደሚወርድ፣

እስከ ልብሱም ዐንገትጌ እንደሚደርስ ውድ ሽቱ ነው።

3 ደግሞም በጽዮን ተራራ ላይ እንደሚወርድ፣

እንደ አርሞንዔም ጠል ነው፤

በዚያእግዚአብሔርበረከቱን፣

ሕይወትንም እስከ ዘላለም አዞአልና።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *