መዝሙር 131

በእግዚአብሔር መታመን

የዳዊት መዝሙረ መዓርግ

1 እግዚአብሔርሆይ፤ ልቤ አልታበየም፤

ዐይኔ ከፍ ከፍ አላለም፤

ሐሳቤ ለዐጒል ትልቅነት አልተነሣሣም፤

ከዐቅሜም በላይ አልተንጠራራሁም።

2 ነገር ግን ነፍሴን ጸጥ፣ ዝም አሰኘኋት፤

ጡት የጣለ ልጅ ዐርፎ እናቱ ላይ እንደሚቀመጥ፣

ነፍሴ ጡት እንዳስተዉት ሕፃን በውስጤ ጸጥ አለች።

3 እስራኤል ሆይ፤ ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም፣

በእግዚአብሔርተስፋ አድርግ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *