ለርዳታ የቀረበ ጥሪ
መዝሙረ መዓርግ
1 እግዚአብሔርሆይ፤ ከጥልቅ ወደ አንተ እጮኻለሁ።
2 ጌታ ሆይ፤ ድምፄን ስማ፤
ጆሮዎችህ የልመናዬን ቃል፣
የሚያዳምጡ ይሁኑ።
3 እግዚአብሔርሆይ፤ ኀጢአትን ብትቈጣጠር፣
ጌታ ሆይ፤ ማን ሊቆም ይችላል?
4 ነገር ግን በአንተ ዘንድ ይቅርታ አለ፤
ስለዚህም ልትፈራ ይገባሃል።
5 እግዚአብሔርንደጅ እጠናለሁ፤ ነፍሴም በትዕግሥት ትጠብቀዋለች፤
በቃሉም ተስፋ አደርጋለሁ።
6 ዘብ ዐዳሪ ንጋትን ከሚጠባበቅ ይልቅ፣
አዎን፤ ዘብ ዐዳሪ ንጋትን ከሚጠባበቅ ይልቅ፣
ነፍሴ ጌታን ትጠባበቃለች።
7 በእግዚአብሔርዘንድ ምሕረት፣
በእርሱም ዘንድ ማዳን አለና፣
እስራኤል ሆይ፤በእግዚአብሔርተስፋ አድርግ።
8 እርሱም እስራኤልን፣
ከኀጢአቱ ሁሉ ያድነዋል።