መዝሙር 128

የጻድቃን በረከት

መዝሙረ መዓርግ

1 እግዚአብሔርንየሚፈሩ ሁሉ፣

በመንገዱም የሚሄዱ የተባረኩ ናቸው።

2 የድካምህን ፍሬ ትበላለህ፤

ትባረካለህ፤ ይሳካልሃልም።

3 ሚስትህ በቤትህ፣

እንደሚያፈራ ወይን ናት፤

ወንዶች ልጆችህ በማእድህ ዙሪያ፣

እንደ ወይራ ተክል ናቸው።

4 እነሆ፤እግዚአብሔርንየሚፈራ ሰው፣

እንዲህ ይባረካል።

5 እግዚአብሔርከጽዮን ይባርክህ፤

በሕይወትህ ዘመን ሁሉ፣ የኢየሩሳሌምን ብልጽግና ያሳይህ፤

6 የልጅ ልጅ ለማየትም ያብቃህ።

በእስራኤል ላይ ሰላም ይውረድ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *