መዝሙር 127

በእግዚአብሔር መታመን

የሰሎሞን መዝሙረ መዓርግ

1 እግዚአብሔርቤትን ካልሠራ፣

ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤

እግዚአብሔርከተማን ካልጠበቀ፣

ጠባቂ በከንቱ ይተጋል።

2 የዕለት ጒርስ ለማግኘት በመጣር፣

ማልዳችሁ መነሣታችሁ፣

አምሽታችሁም መተኛታችሁ ከንቱ ነው፤

እርሱ ለሚወዳቸው እንቅልፍን ያድላልና።

3 እነሆ፤ ልጆችየእግዚአብሔርስጦታ ናቸው፤

የማሕፀንም ፍሬ ከቸርነቱ የሚገኝ ነው።

4 በወጣትነት የተገኙ ወንዶች ልጆች፣

በጦረኛ እጅ እንዳሉ ፍላጾች ናቸው።

5 ኰረጆዎቹ በእነዚህ የተሞሉ፣

የተባረከ ሰው ነው፤

ከጠላቶቻቸው ጋር በአደባባይ በሚሟ

ገቱበት ጊዜ፣ አይዋረዱም።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *