መዝሙር 126

የስደት ተመላሾች መዝሙር

መዝሙረ መዓርግ

1 እግዚአብሔርየጽዮንን ምርኮበመለሰጊዜ፣

ሕልም እንጂ እውን አልመሰለንም።

2 በዚያን ጊዜ አፋችን በሣቅ፣

እንደበታችንም በእልልታ ተሞላ፤

በዚያን ጊዜም በሕዝቦች መካከል፣

“እግዚአብሔርታላቅ ነገር አደረገላቸው” ተባለ።

3 እግዚአብሔርታላቅ ነገር አደረገልን፤

እኛም ደስ አለን።

4 እግዚአብሔርሆይ፤ በነጌቭ እንዳሉ ጅረቶች፣

ምርኳችንን መልስ።

5 በእንባ የሚዘሩ፣

በእልልታ ያጭዳሉ።

6 ዘር ቋጥረው፣

እያለቀሱ የተሰማሩ፣

ነዶአቸውን ተሸክመው፣

እልል እያሉ ይመለሳሉ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *