መዝሙር 122

ኢየሩሳሌም እልል በዪ!

የዳዊት መዝሙረ መዓርግ

1 “ወደእግዚአብሔርቤት እንሂድ” ባሉኝ ጊዜ፣

ደስ አለኝ።

2 ኢየሩሳሌም ሆይ፤ እግሮቻችን ከደጅሽ ውስጥ ቆመዋል።

3 ኢየሩሳሌም እጅግ እንደ ተጠጋጋች፣

ከተማ ሆና ተሠርታለች።

4 ለእስራኤል በተሰጠው ሥርዐት መሠረት፣

የእግዚአብሔርንስም ለማመስገን፣

የእግዚአብሔርነገዶች፣

ወደዚያ ይመጣሉ።

5 በዚያም የፍርድ ዙፋኖች የሆኑት፣

የዳዊት ቤት ዙፋኖች ተዘርግተዋል።

6 እንዲህ ብላችሁ ለኢየሩሳሌም ሰላም ጸልዩ፤

“የሚወዱሽ ይለምልሙ፤

7 በቅጥርሽ ውስጥ ሰላም ይሁን፤

በምሽግሽም ውስጥ መረጋጋት ይስፈን”።

8 ስለ ወንድሞቼና ስለ ባልንጀሮቼ፣

“በውስጥሽ ሰላም ይስፈን” እላለሁ።

9 ስለ አምላካችን ስለእግዚአብሔርቤት፣

በጎነትሽን እሻለሁ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *