መዝሙር 121

የእስራኤል ጠባቂ

መዝሙረ መዓርግ

1 ዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ፤

ረድኤቴ ከወዴት ይመጣል?

2 ረድኤቴ ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ፣

ከእግዚአብሔርዘንድ ይመጣል።

3 እግርህ እንዲሸራተት አይፈቅድም፤

የሚጠብቅህም አይተኛም።

4 እነሆ፤ እስራኤልን የሚጠብቅ፣ አይተኛም፤ አያንቀላፋምም።

5 እግዚአብሔርይጠብቅሃል፤

እግዚአብሔርበቀኝህ በኩል ይከልልሃል።

6 ፀሓይ በቀን አያቃጥልህም፤

ጨረቃም በሌሊት ጒዳት አታመጣብህም።

7 እግዚአብሔርከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል፤

ነፍስህንም ይንከባከባታል።

8 እግዚአብሔርከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም፣

መውጣትህንና መግባትህን ይጠብቃል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *