መዝሙር 120

የሰላም ፀሮች

መዝሙረ መዓርግ

1 በተጨነቅሁ ጊዜ ወደእግዚአብሔርተጣራሁ፤

እርሱም መለሰልኝ።

2 እግዚአብሔርሆይ፤ ከሐሰተኛ ከንፈር፣

ከአታላይ ምላስም አድነኝ።

3 ሐሰተኛ አንደበት ሆይ፤ ምን ይከፈልህ?

ከዚህስ የባሰ ምን ይደረግብህ?

4 በተሳለ የጦረኛ ቀስት፣

በግራር ከሰል ፍም ይቀጣሃል።

5 በሜሼክ እኖራለሁና፣ በቄዳር ድንኳኖች መካከል እቀመጣለሁና ወዮልኝ!

6 ሰላምን በሚጠሉ መካከል፣

ነፍሴ እጅግ ብዙ ጊዜ ኖረች።

7 እኔ ሰላም ፈላጊ ነኝ፤

እነርሱ ግን በተናገርሁ ጊዜ ጠብ ይሻሉ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *