መዝሙር 100

እግዚአብሔርን ለማመስገን የቀረበ ግብዣ

የምስጋና መዝሙር

1 ምድር ሁሉለእግዚአብሔርእልል በሉ፤

2 እግዚአብሔርንበደስታ አገልግሉት፤

በፍስሓ ዝማሬ ፊቱ ቅረቡ።

3 እግዚአብሔርአምላክ መሆኑን ዕወቁ፤

እርሱ ፈጠረን፤ እኛም የእርሱ ነን፤

እኛ ሕዝቡ የማሰማሪያው በጎች ነን።

4 በምስጋና ወደ ደጆቹ፣

በውዳሴም ወደ አደባባዮቹ ግቡ፤

አመስግኑት፤ ስሙንም ባርኩ፤

5 እግዚአብሔርቸር፣ ምሕረቱም ለዘላለም ነውና፤

ታማኝነቱም ከትውልድ እስከ ትውልድ ነው።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *