መዝሙር 95

የየዕለቱ መዝሙር

1 ኑ፤ ደስ እያለንለእግዚአብሔርእንዘምር፤

በድነታችንም ዐለት እልል እንበል።

2 ምስጋና ይዘን ፊቱ እንቅረብ፤

በዝማሬም እናወድሰው።

3 እግዚአብሔርታላቅ አምላክ ነውና፤

ከአማልክትም ሁሉ በላይ ታላቅ ንጉሥ ነው።

4 የምድር ጥልቆች በእጁ ናቸው፤

የተራራ ጫፎችም የእርሱ ናቸው።

5 እርሱ ፈጥሮአታልና፣ ባሕር የእርሱ ናት፤ እጁም የብስን አበጀ።

6 ኑ፤ እናምልከው፤ እንስገድለትም፤

በፈጣሪያችንበእግዚአብሔርፊት እንንበርከክ፤

7 እርሱ አምላካችን ነውና፤

እኛም በእጁ ጥበቃ ሥር ያለን በጎቹ፣

የመሰማሪያውም ሕዝብ ነን።

ዛሬ ድምፁን ብትሰሙ፣

8 በምድረ በዳ በነበራችሁበት ቀን በማሳህ፣

በመሪባምእንዳደረጋችሁት፣ ልባችሁን አታደንድኑ።

9 ሥራዬን ቢያዩም፣

አባቶቻችሁ በዚያ ፈተኑኝ፤ ተፈታተኑኝም።

10 ያን ትውልድ አርባ ዓመት ሙሉ ተቈጣሁት፤

እኔም፣ “ልቡ የሸፈተ ሕዝብ ነው፤

መንገዴንም አላወቀም” አልሁ።

11 ስለዚህ፣ “ፈጽሞ ወደ ዕረፍቴ አይገቡም” ብዬ፣

በቍጣዬ ማልሁ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *