መዝሙር 93

የእግዚአብሔር ግርማ

1 እግዚአብሔርነገሠ፤ ግርማንም ተጐናጸፈ፤

እግዚአብሔርግርማን ለበሰ፤

ብርታትንም ታጠቀ፤

ዓለም እንዳትናወጥ ጸንታለች፤

ማንም አይነቀንቃትም።

2 ዙፋንህ ከጥንት ጀምሮ የጸና ነው፤

አንተም ከዘላለም እስከ ዘላለም አለህ።

3 እግዚአብሔርሆይ፤ ወንዞች ከፍ አደረጉ፤

ወንዞች ድምፃቸውን ከፍ አደረጉ፤

ወንዞች የሚያስገመግም ማዕበላቸውን ከፍ አደረጉ።

4 ከብዙ ውሆች ድምፅ ይልቅ፣

ከባሕርም ሞገድ ይልቅ፣

ከፍ ብሎ ያለውእግዚአብሔርኀያል ነው።

5 ሥርዐትህ የጸና ነው፤

እግዚአብሔርሆይ፤ እስከ ዘላለሙ፣

ቤትህ በቅድስና ይዋባል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *