ሙሱናን ዳኞች
የአሳፍ መዝሙር
1 እግዚአብሔር በአማልክት ጉባኤ መካከል ተሰየመ፤
በአማልክትም ላይ ይፈርዳል፤ እንዲህም ይላል፦
2 “ፍትሕን የምታጓድሉት እስከ መቼ ነው?
ለክፉዎች የምታደሉትስ እስከ መቼ ነው?ሴላ
3 ለዐቅመ ቢሶችና ለድኻ አደጎች ፍረዱላቸው፤
የችግረኛውንና የምስኪኑን መብት አስከብሩ።
4 ወገን የሌለውንና ችግረኛውን ታደጉ፤
ከግፈኛውም እጅ አስጥሏቸው።
5 “ዕውቀትም ማስተዋልም የላቸውም፤
በጨለማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይመላለሳሉ፤
የምድርም መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ።
6 “እኔም፤ ‘እናንተ አማልክት ናችሁ፤
ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ’ አልሁ።
7 ነገር ግን እንደ ማንኛውም ሰው ትሞታላችሁ፤
እንደ ማንኛውም ገዥ ትወድቃላችሁ።”
8 አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ በምድር ላይ ፍረድ፤
ሕዝቦች ሁሉ ርስትህ ናቸውና።