መዝሙር 47

እግዚአብሔር፣ የእስራኤል ንጉሥ የዓለም ጌታ

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1 ሕዝቦች ሁላችሁ እጆቻችሁን አጨብጭቡ፤

ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር እልል በሉ።

2 በምድር ሁሉ ላይ ታላቅ የሆነው ንጉሥ፣

ልዑልእግዚአብሔርየሚያስፈራ ነውና።

3 ሕዝቦችን ከእኛ በታች አደረገ፤

መንግሥታትንም ከእግራችን ሥር አስገዛልን።

4 ለሚወደው ለያዕቆብ ክብር የሆነችውን፣

ርስታችንን እርሱ መረጠልን።ሴላ

5 አምላክ በእልልታ፣

እግዚአብሔርበመለከት ድምፅ ዐረገ።

6 አምላካችንን አወድሱት፤ አወድሱት፤

ንጉሣችንን አወድሱት፤ አወድሱት፤

7 እግዚአብሔርየምድር ሁሉ ንጉሥ ነውና፤

ምርጥ ዝማሬአቅርቡለት።

8 እግዚአብሔር በሕዝቦች ላይ ነግሦአል፤

እግዚአብሔር በተቀደሰ ዙፋኑ ላይ ተቀምጦአል።

9 ከአብርሃም አምላክ ሕዝብ ጋር፣

የሕዝቦች መኳንንት ተሰበሰቡ፤

የምድር ነገሥታትየእግዚአብሔር ናቸውና፤

እርሱም እጅግ ከፍ ከፍ ያለ ነው።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *