መዝሙር 43

በስደት ላይ ያለ ሌዋዊ ልቅሶ

1 አምላክ ሆይ፤ ፍረድልኝ፤

ከጽድቅ ከራቀ ሕዝብ ጋር ተሟገትልኝ፤

ከአታላዮችና ከክፉዎች ሰዎችም አድነኝ።

2 አምላክ ሆይ፤ አንተ ብርታቴ ነህና፣

ለምን ተውኸኝ?

ጠላትስ እያስጨነቀኝ፣

ለምን በሐዘን እመላለሳለሁ?

3 ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤

እነርሱ ይምሩኝ፤

ወደ ተቀደሰው ተራራህ፣

ወደ ማደሪያህ ያድርሱኝ።

4 እኔም ወደ እግዚአብሔር መሠዊያ አቀናለሁ፤

ፍጹም ደስታዬ ወደ ሆነው አምላክ እሄዳለሁ፤

እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፣

በበገና አመሰግንሃለሁ።

5 ነፍሴ ሆይ፤ ለምን ትተክዢያለሽ?

ለምንስ በውስጤ ትታወኪያለሽ?

ተስፋሽን በአምላክ ላይ አድርጊ፤

አዳኜና አምላኬን፣

ገና አመሰግነዋለሁና።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *