መዝሙር 23

መልካሙ እረኛ

የዳዊት መዝሙር

1 እግዚአብሔርእረኛዬ ነው፤

አንዳች አይጐድልብኝም።

2 በለመለመ መስክ ያሳርፈኛል፤

በዕረፍት ውሃ ዘንድ ይመራኛል፤

3 ነፍሴንም ይመልሳታል።

ስለ ስሙም፣

በጽድቅ መንገድ ይመራኛል።

4 በሞት ጥላ ሸለቆ ውስጥ፤

ብሄድ እንኳ፣

አንተ ከእኔ ጋር ስለ ሆንህ፣

ክፉን አልፈራም፤

በትርህና ምርኵዝህ፣

እነርሱ ያጽናኑኛል።

5 ጠላቶቼ እያዩ፣

በፊቴ ማዕድ አዘጋጀህልኝ፤

ራሴን በዘይት ቀባህ፤

ጽዋዬም ሞልቶ ይፈስሳል።

6 በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣

በጎነትና ምሕረት በእርግጥ ይከተሉኛል፤

እኔምበእግዚአብሔርቤት፣

ለዘላለም እኖራለሁ።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *