መዝሙር 20

ጸሎት ለንጉሡ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር

1 እግዚአብሔርበጭንቅ ቀን ይስማህ፤

የያዕቆብም አምላክ ስም ይጠብቅህ።

2 ከመቅደሱ ረድኤት ይላክልህ፤

ከጽዮንም ደግፎ ይያዝህ።

3 ቍርባንህን ሁሉ ያስብልህ፤

የሚቃጠል መሥዋዕትህን ይቀበልልህ።ሴላ

4 የልብህን መሻት ይስጥህ፤

ዕቅድህን ሁሉ ያከናውንልህ።

5 በአንተ ድል ደስ ይበለን፤

በአምላካችን ስም አርማችንን ከፍ እናደርጋለን፤

እግዚአብሔርየለመንኸውን ሁሉ ይፈጽምልህ።

6 እግዚአብሔር፣የቀባውን እንደሚያድን

አሁን ዐወቅሁ፤

የማዳን ኀይል ባለው ቀኝ እጁ፣

ከተቀደሰው ሰማይ ይመልስለታል።

7 እነዚህ በሰረገላ፣ እነዚያ በፈረስ ይመካሉ፤

እኛ ግን ትምክህታችን የአምላካችንየእግዚአብሔርስም ነው።

8 እነርሱ ተሰነካክለው ወደቁ፤

እኛ ግን ተነሣን፤ ጸንተንም ቆምን።

9 እግዚአብሔር ሆይ፤ ንጉሥን አድን፤

እኛም በጠራንህ ቀን ስማን።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *