መዝሙር 3

የመከራ ተቀባዩ የጧት ጸሎት

ዳዊት ከልጁ ከአቤሰሎም በሸሸ ጊዜ የዘመረው መዝሙር

1 እግዚአብሔርሆይ፤ ጠላቶቼ ምንኛ በዙ

ስንቱስ በእኔ ላይ ተነሣ!

2 ብዙዎች ነፍሴን፣ “እግዚአብሔር

አይታደግሽም” አሏት።ሴላ

3 እግዚአብሔርሆይ፤ አንተ ግን ዙሪያዬን

የምትከልል ጋሻ ነህ፤

ክብሬና፣ ራሴንም ቀና ቀና

የምታደርግ አንተ ነህ።

4 ወደእግዚአብሔርድምፄን ከፍ አድርጌ እጮሃለሁ፤

እርሱም ከተቀደሰ ተራራው ይመልስልኛል።ሴላ

5 እተኛለሁ፤ አንቀላፋለሁ፤

እግዚአብሔርደግፎ ይዞኛልና እነቃለሁ።

6 በየአቅጣጫው የከበበኝን፣

አእላፍ ሕዝብ አልፈራም።

7 እግዚአብሔርሆይ ተነሥ!

አምላኬ ሆይ፤ ታደገኝ፤

የጠላቶቼን ሁሉ መንጋጋ ትመታለህ፤

የክፉዎችንም ጥርስ ትሰባብራለህ።

8 ማዳንየእግዚአብሔርነው፤

በረከትህ በሕዝብህ ላይ ይሁን።ሴላ

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *