መዝሙር 1

ሁለቱ መንገዶች

1 በክፉዎች ምክር የማይሄድ፣

በኀጢአተኞች መንገድ የማይቆም፣

በፌዘኞችም ወንበር የማይቀመጥ፣

ሰው ብፁዕ ነው።

2 ነገር ግን ደስ የሚሰኘውበእግዚአብሔርሕግ ነው፤

ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያሰላስለዋል።

3 እርሱም በወራጅ ውሃ ዳር እንደ ተተከለች፣

ፍሬዋን በየወቅቱ እንደምትሰጥ፣

ቅጠሏም እንደማይጠወልግ ዛፍ ነው፤

የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።

4 ክፉዎች ግን እንዲህ አይደሉም፤

ነገር ግን ነፋስ ጠራርጎ እንደሚወስደው፣

ገለባ ናቸው።

5 ስለዚህ ክፉዎች በፍርድ ፊት፣

ኀጢአተኞችም በጻድቃን ማኅበር መቆም አይችሉም፤

6 እግዚአብሔርየጻድቃንን መንገድ ይጠብቃልና፤

የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *